በጦርነቱ የተጎዱ ዜጎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ የሁሉንም ርብርብና ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገለጸ
******
(ኢ ፕ ድ)
በሀገሪቱ ሰሜናዊ ክፍል ለሁለት ዓመታት ሲካሄድ በቆየው ጦርነትና በተለያዩ አካባቢዎች በተፈጠሩ ግጭቶች የተጎዱ ዜጎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ የሁሉንም ርብርብ የሚያሻው መሆኑን ሆልስቲክ ፍሪደም ኢንተርናሽናል መስራች እና ፕሬዚዳንት ዶክተር አጊቱ ወዳጆ አስታወቁ፡፡
በሀገሪቱ እውነተኛ እርቅና ሰላም እንዲመጣም ሁሉም ጥፋቶች በግልፅ የሚነገሩበትና በጉዳዮች ይቅርታ የሚጠይቁበት ሥርዓት ሊፈጠር እንደሚገባም አመልክተዋል።
ዶክተር አጊቱ ወዳጆ ለኢፕድ እንዳስታወቁት፤ ከሁሉም ጦርነት በኋላ ትልቁና ከባዱ ችግር ተፈናቃዮችን ወይም በግጭቱ ተጎጂ የነበሩ ሰዎችን መልሶ ማቋቋም ነው። ይህም በሀገር ኢኮኖሚ፤ ማህበራዊ ግንኙነትና ፖለቲካው ላይ የሚኖረው አሉታዊ ተፅዕኖ ከፍተኛ ነው። ተጎጂዎቹን መልሶ የማቋቋሙ ሥራ ጊዜ የሚሰጠው ጉዳይ ባለመሆኑ ሁሉም የሀገሪቱ ህዝብ ርብርብ ሊያደርግ ይገባል።
‹‹ይህንን ችግር ለመፍታት ከሴንትራል አሜሪካ ተሞክሮ መቅሰም አለብን ብዬ አምናለሁ›› ያሉት ዶክተር አጊቱ፤ በመጀመሪያ የፖለቲካ አንጃዎች እርቅ ከፈፀሙ በኋላ እርዳታ አሰባስበው ተፈናቃዮችን መልሶ የማቋቋም ስራ በመስራታቸው መፈናቀሉ ሊያደርሰው የሚችለውን...